ኢንስቲትዩቱ ያለውን ውስን የተሸከርካሪ ሀብት እና የአገልግሎታቸውን ዘመን ከግምት ውስጥ
በማስገባት በአግባቡ ለመገልገል፤ በብልሽት ወቅት የሚጠይቁትን ከፍተኛ የሆነ የጥገና ወጪ
ለመቀነስ፤ በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የነዳጅ እና ቅባት ወጪን ከግምት ውስጥ ያስገባና
ወጪ ቆጣቢ የሆነ የአሰራር ስርአትን በተቋም ደረጃ ተግባራዊ ለማድረግ እንዲቻል፤ እንዲሁም
ኢንስቲትዩቱ በአዲስ መልክ በማቋቋሚያ ደንብ ቁጥር 527/2015 አንቀጽ 6 ንዑስ አንቀጽ
21 በተሰጠው ተቋማዊ የአሰራር ስርዓቶችን የመዘርጋት ሥልጣንና ተግባር መሠረት
በማድረግ በገንዘብ ሚኒስቴር በወጣው የፌደራል መንግስት ተሸከርካሪዎች ስምሪትና
አጠቃቀም መመሪያ ቁጥር 32/2004 መሰረት ይህን የተሽከርካሪዎች ስምሪትና አጠቃቀም
መመሪያ አውጥቷል፡፡