በተቋሙ የበጀት ዓመቱ የ1ኛ ሩብ ዓመትጠቅላላ የማኔጅመንት መደበኛ ስብሰባ ተካሄደ

  • Post author:
  • Post category:News
  • Post comments:0 Comments

***********************************************የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩትጥቅምት 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የ2017 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት የጠቅላላ ማኔጅመንት መደበኛ ስብሰባ ጥቅምት 18 ቀን 2017 ዓ.ም በተቋሙ ሕሩይ አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ስብሰባውን በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የከፈቱት በተቋሙ የም/ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ድሪባ ገለቲ ሲሆኑ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ንጉሤ ደቻሳ በፓዎር ፖይንት የታገዘ የመክፈቻ ንግግር አቅርበዋል፡፡ በመቀጠልም በዋናው መ/ቤት የሴክተር ዳይሬክተሮች በተቀመጠላቸው መርሀ-ግብር መሠረት የበጀት ዓመቱን የ1ኛ ሩብ ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ ሪፖርቱ የምርምር ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ (የምርምር ስራና ውጤቶችን) በተመለከተ፤ የቴክኖሎጂ ጥበቃና ሽግግር ዕቅድ አፈጻጸምን (መነሻ ቴክኖሎጂ፣ ሰርቶ ማሳያ፣ ስልጠና፣ ቴክኖሎጂ ብዜት፣ ቴክኖሎጂ ማስፋትን) በተመለከተ፤ የዘርፈ-ብዙ (cross-cutting) ስራዎች አፈጻጸምን በተመለከተ፤ የአስተዳደርና የማኔጅመንት ዕቅድ አፈጻጸምን በተመለከተ፤ (የፋይናንስ አፈፃፀም፣ የሰው ሀብት አስተዳደር፣ የመሰረተ ልማት ሂደቶችን እና የውጭ ትብብር)፤ እንዲሁም የዋና ዋና የአፈጻጸም ማነቆዎች/ተግዳሮቶች በሪፖርት ለግምገማ ቀርበዋል፡፡ በሪፖርቱ መሠረት ውይይት ከተካሄደ በኋላ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮችና በሥራ ላይ ባጋጠሙ ችግሮች ላይ የመፍትሄ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

Continue Readingበተቋሙ የበጀት ዓመቱ የ1ኛ ሩብ ዓመትጠቅላላ የማኔጅመንት መደበኛ ስብሰባ ተካሄደ

Avocado Feasibility and Suitability Study Consultative and Validation Workshop Held

  • Post author:
  • Post category:News
  • Post comments:0 Comments

October 31, 2024EIAR, Addis AbabaAvocado feasibility and suitability study, consultation, and validation session were held at EIAR's HiruyHall. In his welcoming remarks, Mr. Abdella Negash, Lead Executive for Horticulture Development…

Continue ReadingAvocado Feasibility and Suitability Study Consultative and Validation Workshop Held

የዋና ዳይሬክተሮች የሽኝት እና የአቀባበልመርሐ-ግብር ተካሄደ

  • Post author:
  • Post category:News
  • Post comments:0 Comments

****************************************የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩትጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም.በኢንስቲትዩቱ ለአራት ዓመታት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ክቡር ዶ/ር ፈቶ ኢስሞ የሽኝት ፕሮግራም ተደረገላቸው፡፡ የሽኝት ፕሮግራሙ ዶ/ር አበራ ደሬሳ የተቋሙ የቦርድ ሰብሳቢ፤ ዶ/ር ብርሃኔ ገ/ኪዳን የተቋሙ የቦርድ አባል፤ የማዕከላት አመራሮች፤ ሠራተኞችና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት ተከናውኗል፡፡ በአንፃሩም አዲስ ለተሾሙት ፐሮፌሰር ንጉሴ ደቻሳ የአቀባበል መርሐ-ግብር ተከናውኗል፡፡ በሽኝት እና በአቀባበል መርሐ-ግብሩ ላይ የኢንስቲትዩቱ የም/ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ድሪባ ገለቲ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ሽኝት ለሚደረግላቸው ለክቡር ዶ/ር ፈቶ ኢስሞ የመልካም ዕድል ምኞት አዲስ ለተሾሙት ፐሮፌሰር ንጉሴ ደቻሳ ደግሞ መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንላቸው በራሣቸውና በተቋሙ ሠራተኞች ስም ምኞታቸውን ገልፀዋል፡፡በመርሐ-ግብሩ የተቋሙ የዋና መስሪያ ቤትና የማዕከላት ሰራተኞችና አመራሮች ለክቡር ዶ/ር ፈቶ ኢስሞ የስጦታ ማስታወሻ አበርክተውላቸዋል፡፡

Continue Readingየዋና ዳይሬክተሮች የሽኝት እና የአቀባበልመርሐ-ግብር ተካሄደ

ማዕከሉ የመስክ ቀን አካሄደ

  • Post author:
  • Post category:News
  • Post comments:0 Comments

ጥቅምት 16 ቀን 2017 ዓ.ም. የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት/አሰላ በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የቁሉምሳ ግብርና ምርምር ማዕከል በለሙ እና ቢልቢሎ ወረዳ በቆጂ ከተማ እንዲሁም በምርምር ማዕከሉ የተለያዩ የባለድርሻ አካላት በተገኙበት ማለትም የኦሮሚያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፤ የአሰላ ብቅል ፋብሪካ ኃላፊዎች፣ የአሰላ ከተማ አስተዳደር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊዎች፤ የማዕከሉ ተመራማሪዎች እንዲሁም የዋናው መ/ቤት አመራሮች በተገኙበት የመስክ ጉብኝት አካሂዷል፡፡ ጉብኝቱ በአካባቢው ባህል መሠረት በአገር ሽማግሌዎች ምርቃት ተጀምሯል፡፡  የመስክ ጉብኝት ቀንኑ አስመልክቶ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የቁሉምሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር አቶ ደበሌ ደበላ ሲሆኑ የመስክ ጉብኝቱን ለመታደም የተገኙትን እንግዶች አመስግነዋል፡፡ ቀጥለውም የቁሉምሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ከተቋቋመበት እ.ኤ.አ ከ1960ዎቹ ጀምሮ በተለይ በዳቦ ስንዴ፤ በብቅል እና በምግብ ገብስ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ከፍተኛ ውጤቶችን ሲያስመዘግብ ቆይቶ በአሁኑ ወቅት በአገር ደረጅ የስንዴ የልህቀት ማዕከል እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ በመቀጠልም በመጀመሪያ የመስክ ጉብኝት በተካሄደበት የቦቆጂ ንዑስ ጣቢያ የስንዴ እና የገብስ የመነሻ ዘር ማባዣ ማሣን እንዲሁም የአፈሩን ለምነት ለመጠበቅ ያስችል ዘንድ በፈረቃ የሚለሙ የባቄላ፣ የአተር እና የተልባ ማሣዎች ለጉብኝት መቅረባቸውንና የምርታማነት መጠንን በዝርዝር አሰረድተዋል፡፡  በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የም/ም ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ድሪባ ገለቲ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ኢንስቲትዩቱ በአገራችን ከሚገኙ ትላልቅ ተቋማት አንዱ ሲሆን ቴክኖሎጂ በመልቀቅ፤ የመነሻ ዘር በማባዛትና በማሰራጨት፤ ቴክኖሎጂ በማስተዋወቅ እና የአቅም ግንባታ በመገንባት ረገድ የተሰጠውን ተለልዕኮ በተግባር ከሚወጡት ዋነኛው ነው ብለዋል፡፡ የቁሉምሳ የግብርና ምርምር ማዕከልም በኢንስቲቲዩቱ ስር ከሚገኙ ትልልቅ ማዕከላት ትልቁ እንደዚሁም ከፍተኛ ስራዎችን ከሚሰሩት መካከል አንዱ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ በማዕከሉ ግቢ እና በሌሎች ንዑስ ጣቢዎች ጉብኝት ከተካሄደ በኋላ ከተለያዩ የባለድርሻ አካላት አበረታችና ገምቢ ግብረ-መልስ ቀርቧል፤ በመጨረሻም ውይይት የተደረገ ሲሆን በኢንስቲትዩቱ የም/ም/ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ድሪባ ገለቲ ሰፋ ያለ ማብራሪያና የስራ መመሪያ ተሰጥቶ የዕለቱ መርሐ-ግብር ተጠናቋል፡፡

Continue Readingማዕከሉ የመስክ ቀን አካሄደ

Mirimir is a quarterly newsletter of the Ethiopian Institute of Agricultural Research

The Ethiopian Institute of Agricultural Research is a federal research institute that conducts research in various spectrums of agricultural disciplines to provide demand-driven and market-competitive agricultural technologies that contribute to…

Continue ReadingMirimir is a quarterly newsletter of the Ethiopian Institute of Agricultural Research

የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩቱ የመኖሪያ ቤትና የመገልገያ ዕቃዎችድልድልና አጠቃቀም መመሪያ ቁጥር …. / 2016

ኢንስቲትዩቱ የሠራተኞችን ዕውቀትና ክህሎት በተሻለ ሁኔታ ለመጠቀም ከሚገለገልባቸውስልቶች መካከል ለምርምር ሥራ ምቹ የሥራ አካባቢን ከመፍጠር ጋር ተያይዞ ሠራተኞችምርምሩ በሚካሄድበት አካባቢ በቅርበት በመኖር የምርምሩን ሥራ በተረጋጋ ሁኔታእንዲያከናውኑ የመኖሪያ ቤት በተገነባላቸው ማዕከላት…

Continue Readingየኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩቱ የመኖሪያ ቤትና የመገልገያ ዕቃዎችድልድልና አጠቃቀም መመሪያ ቁጥር …. / 2016

የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የደንብ ልብስ አጠቃቀም መመሪያ…/2016

የፌዴራል መንግሥት መ/ቤቶችና ተቋማት እንደተቋማቸው የሥራ ባህሪያት የራሳቸውንየሥራ ልብስ፤ የሥራ መሣሪያና ቁሳቁሶችን አጠቃቀም መመሪያ አዘጋጅተው መጠቀምእንዲችሉ በነሐሴ 14 ቀን 2000 ዓ.ም በቁጥር መ.30/ጠ57/20/334 ከቀድሞው የፌዴራልሲቪል ሰርቪስ ኤጀንሲ በተጻፈ ደብዳቤ በተሰጠው…

Continue Readingየኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የደንብ ልብስ አጠቃቀም መመሪያ…/2016

የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የተሽከርካሪዎች ስምሪትናአጠቃቀም መመሪያ ቁጥር ……/2016

ኢንስቲትዩቱ ያለውን ውስን የተሸከርካሪ ሀብት እና የአገልግሎታቸውን ዘመን ከግምት ውስጥበማስገባት በአግባቡ ለመገልገል፤ በብልሽት ወቅት የሚጠይቁትን ከፍተኛ የሆነ የጥገና ወጪለመቀነስ፤ በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የነዳጅ እና ቅባት ወጪን ከግምት ውስጥ ያስገባናወጪ ቆጣቢ…

Continue Readingየኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የተሽከርካሪዎች ስምሪትናአጠቃቀም መመሪያ ቁጥር ……/2016

የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የምርምር አመራር ምደባ መመሪያቁጥር …. /2016

የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የአገራችንን የግብርና ክፍለ ኢኮኖሚ ለማሳደግየሚያስችሉ የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለግብርና ልማት ተጠቃሚዎች በማድረስ ረገድከፍተኛ ሀገራዊ ተልዕኮ የተሰጠው ተቋም ሲሆን ኢንስቲትዩት ሲሆን ይህንኑ ተልዕኮ ለመወጣትተቋማዊ አደረጃጀቱን በየጊዜው እየፈተሸ…

Continue Readingየኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የምርምር አመራር ምደባ መመሪያቁጥር …. /2016